ከክረምቱ የተጠናከረ ዝናብ ጋር በተያያዘ    የለገዳዲ ግድብ በመሙላቱ የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ከነሐሴ 13 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ክረምቱ መጨረሻ ድረስ ደለልና ትርፍ ውሃ ያስወግዳል፡፡ በመሆኑም ከግድቡ በታችኛው ተፋሰስ አካባቢ የምትገኙ ነዋሪዎች እና ተቋማት በሰው፣ በቤት እንስሳም ሆነ በንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ከወዲሁ ቅድመ ጥንቃቄ እንድታደርጉ ያሳውቃል፡፡

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን