የባለሥልጣን መ/ቤቱ በታህሳስ ወር 2010 ዓ.ም በሪፖርተር ጋዜጣ በተለያዩ የሥራ መደቦች የውጪ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት መስፈርቱን ያሟሉ ዕጩዎችን በፈተና አወዳድሮ በመለየት ቅጥር መፈጸሙ ይታወሳል፡፡

ይሁን እንጅ የፈተናው ውጤት እንደታወቀ የተወሰኑ አመልካቾች ቅሬታ በማቅረባቸው ጉዳዩ በኮሚቴ ታይቶ ከተጣራ በኋላ የውጤት ማስተካከያ ተደርጎና በመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ ጸድቋል፡፡

በመሆኑም በውጤታችሁ ቅደም ተከተል መሠረት በተገኙት ክፍት የሥራ መደቦች ልክ የሰው ኃይል እንዲሟላ ጥሪ ማስተላለፍ አስፈልጓል፡፡

በዚሁም መሠረት የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ ማስታወሻ ጋር ተያይዞ የምትገኙት ዕጩ ተወዳዳሪዎች ከዋናው መ/ቤት እና ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ተጨማሪ የባለሙያ ቅጥር ጥያቄ በመቅረቡ በቅድሚያ ከሥራው ጋር የተዛመደ ሥልጠና በመስጠት ቅጥሩ እንዲፈጸም ተወስኗል፡፡ በመሆኑም ሥልጠናው የሚጀመረው ሐሙስ ነሐሴ 17 ቀን 2010 ዓ.ም ከጥዋቱ 2፡30 ሰዓት በመሆኑ በዋናው መ/ቤት አዳራሽ እንድትገኙ ጥሪያችንን እያስተላለፍን፤ በቀጣይም ተመሳሳይ ክፍት የሥራ መደብ ሲፈጠር ቀሪዎቹን ዕጩ ተወዳዳሪዎች በውጤታችሁ ቅደም ተከተል መሠረት ጥሪ በማስተላለፍ ቅጥሩን የምንፈጽም መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ተ.ቁ የሚቀጠረው ባለሙያ ስም የሚቀጠሩበት የሥራ መደብ መጠሪያ የሥራ ዘርፍ ምርመራ
1 መሠረት የሽጥላ ገ/ማሪያም መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
2 ወይንሸት በርታ ደዴቦ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
3 አሮን ብርሃኑ ደገፋ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
4 ሜሪ አመንሲሳ ቶላ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
5 ናትናኤል ጤናው ዘለቀ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
6 ስዩም ኃይሌ በርሄ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
7 ንጉሴ ሞላ መንግስቴ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
8 ነጻነት ታደለ አለሙ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
9 ያሬድ አለምነው ባዩ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
10 ደምረው ለገሰ ዳዲ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
11 ዝይን መለሰ አደራ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
12 ሰሎሞን ዳዊት አምባው መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
13 ዘመኑ አማረ መንግስቱ መሐንዲስ I(ለውኃ) ውኃ ዘርፍ
14 ማክቤል ባሻው ገ/መድህን መሐንዲስ I(ለፍሳሽ) ፍሻስ ዘርፍ
15 ወ/ገብርኤል ሐጎስ ወ/ሊባኖስ መሐንዲስ I(ለፍሳሽ) ፍሻስ ዘርፍ
16 ሳሌም አሌሮ ሚናሞ መሐንዲስ I(ለፍሳሽ) ፍሻስ ዘርፍ
17 ህይወት ይስማው መኮንን መሐንዲስ I(ለፍሳሽ) ፍሻስ ዘርፍ
18 ሱሌይማን መሀመድ ሀሰን መሐንዲስ I(ለፍሳሽ) ፍሻስ ዘርፍ
19 መሠረት አራርሳ ማኬ መሐንዲስ I(ለፍሳሽ) ፍሻስ ዘርፍ
20 መርሐዊት ቴዎድሮስ በላይ መሐንዲስ I(ለፍሳሽ) ፍሻስ ዘርፍ
21 ማህደር ደረጀ አስጢፋኖስ መሐንዲስ I(ለፍሳሽ) ፍሻስ ዘርፍ