የፍሳሽ መሰረተ ልማቶቻችን ላይ ከፍተኛ አደጋ ተጋርጧል ፡፡

የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ በአለም ባንክ ብድር ያሰራው የቃሊቲ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ በሙሉ አቅሙ እንዲያጣራ 80 ኪሎ ሜትር መስመር ተዘርግቶ የቤት ለቤት ቅጥያ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ፡፡ በተፋሰሱ ስር የሚገኙ ነዋሪዎችን የዘመናዊ ፍሳሽ አወጋገድ ስርዓት ተጠቃሚ ለማድረግ በተዘረጋ 80 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ ማሰባሰቢያ መስመር ላይ ከ550 በላይ ማንሆል ተሰርቶ የብረት ክዳን...

በአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት በመኖሪያ ቤት የውሃ ቆጣሪ ወስደው በንግድ ስራ የተሰማሩ 15 ደንበኞች በፍተሻ ማግኘቱን ይፋ አደረገ፡፡

ደንበኞቹ በየካ ፣በአራዳ እና በጉለሌ ክ/ከተማ ስር የሚገኙ 15 ንግድ ቤት ሆነው በመኖሪያ ቤት ታሪፍ ሲከፍሉ የነበሩ ናቸው፡፡ ለዚህም ተግባራቸው ቅ/ጽ/ቤቱ የንግድ ፈቃዳቸውን በማየት አገልግሎት መስጠት ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ ወደ ኋላ በማስላት 47, 511, ብር እንዲከፍሉ ማድረጉን በቅ/ጽ/ቤቱ የውሃ ደንበኞች አገልግሎት ንዑስ የስራ ሂደት መሪ አቶ ሙሉጌታ ዓለማየሁ ተናግረዋል፡፡ አቶ ሙሉጌታ አክለዉም ደንበኛች በመኖሪያ...

ውሃን በቁጠባ ለመጠቀም ሆነ ወጪ ለመቀነስ የመልሶ መጠቀም አሰራር መዘርጋቱ በእጅጉ ጠቅሞናል አሉ በማህበር ተደራጅተው በተሸከርካሪ እጥበት የተሰማሩ አንድ አንድ ማበራት ፡፡

የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት በስሩ ካሉ እና ህጋዊ ከሆኑ ሰባት ማህበራ ጋር በመነጋገር በቀላሉ ውሃን መልሶ በመጠቀም እንዲገለገሉ ግንዛቤ በመፍጠር ወደ ስራ ገብቷል ፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ሶስቱ ሙሉ በሙሉ መጠቀም የጀመሩ ሲሆን አራቱ ማህበራት ደግሞ በሂደት ላይ ናቸው፡፡ ከነዚህ መካከል በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ አራት የሚገኝ ሚካኤልና ጓደኞቹ የተሸከርካሪ እጥበት ማህበር አንዱ ነው፤የማህበሩ...

ንብረትነቱ የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን የሆነው የፍሳሽ መሰረተ ልማት ላይ ባእድ ነገር ሲጨምሩ የተገኙ ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት የፋብሪካ ተረፈ ምርት በቦቴ ተሸከርካሪ በማጓጓዝ እና በባለስልጣኑ የፍሳሽ መስመር ውስጥ በመድፋታቸው ነው፡፡ በተደጋጋሚ በፍሳሽ መሰረተ ልማቱ ላይ የፋብሪካ ፍሳሽ ተረፈ ምርት በመደፋቱ የመዲናዋን ፍሳሽ አወጋገድ ዘመናዊ ለማድረግ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው የቃሊቲ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ የኤሌክትሮ ሜካኒካል እና ባዮሎጂካል ክፍሎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል፡፡ ይህንንም ችግር ለመቅረፍ...

በአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን ከፍተኛ የውሃ መስመር ላይ ጉዳት ያደረሱ የኮንስትራክሽን ድርጅቶች 2 ሚሊዮን ብር በላይ ካሳ እንዲከፍሉ ተወሰነባቸው፡፡

ውሳኔውን ያስተላለፉት የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ እና የአቃቂ ምድብ ችሎት ናቸው፡፡ ሲሲሲሲ በመባል የሚታወቀው የቻይና ኮሙኒኬሽን እና ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ቃሊቲ በሚገኛው የባለስልጣኑ ከባድ መስመር ላይ ጉዳት ማድረሱን የተመለከተው የልደታ ምድብ ችሎት ድርጅቱ ላደረሰው ጉዳት እና ኪሳራ አንድ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሀምሳ ሁለት ሺ ሁለት መቶ አርባ ሰባት ብር (1,752,247) ካሳ እንዲከፍል ውሳኔ...