እንኳን ደህና መጣችሁ!!!

የድሬ ግድብ

ግንባታው በ1991 ተጠናቀቀ

21 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ ጥሬ ውሃ የመያዝ አቅም አለው

የገፈርሣ ግድብና ማጣሪያ ጣቢያ

ግንባታው በ1948 ተጠናቀቀ

በ2001 በጀት ዓመት የጥገና ሥራ ከተካሔደለት ጥሬ ውሃ የመያዝ አቅሙ ወደ 9.5 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ያደገ ሲሆን ውሃ የማምረት አቅሙም በቀን 30ሺ ሜትር ኪዩብ ነው

ለገዳዲ ግድብ

በ1963 ተመሠረተ

47 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ጥሬ ውሃ የመያዝ አቅም አለው

በ1977 ማስፋፊያ ከተደረገለት በኋላና በ1990ዎቹ አጋማሽ የኬሚካል አጠቃቀሙን ማሻሻል እና የሥርጭት መሥመሩን መቀየር ያስቻለ የዕድሳት ሥራ ከተከናወነለት በኋላ ዕለታዊ ውሃ የማማረት አቅሙ በቀን 165ሺ ሜትር ኪዩብ ደርሶ ነበር፡፡ ከዚህ በኋላም በ2007 ዓ.ም. የድሬ ግድብን ውሃ የመያዝ አቅም መጨመርና የለገዳዲ ማጣሪያ ጣቢያን ውሃ የማምረት አቅም በ30ሺ ሜትር ኪዩብ ውሃ ማሳደግ ያስቻለ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ተካሒዷል፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ወቅት ከግድብ በየዕለቱ 195ሺ ሜትር ኪዩብ ውሃ ይመረታል፡፡

የከርሠ ምድር ውሃ

ከ1987 ዓ.ም. ወዲህ በከተማዋ ከ100 በላይ ጥልቅና መካከለኛ ጉድጓዶች ተቆፍረው አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡በአሁኑ ወቅት በከተማዋ በቀን ከሚመረተው 608ሺ ሜትር ኪዩብ ውሃ ውስጥ 413ሺ ሜትር ኪዩብ (67.9%) ያህሉ ከከርሠ ምድር ውሃ መገኛዎች የሚመረት ነው፡፡

የፍሳሽ ማስወገጃ መኪኖች

ያለቦትን የውሃ ክፍያ በቀላሉ ይመልከቱ!

የቢል መረጃ
R||divi||400

ራዕይ

በ2022 ዓ.ም. ተቋማችን በሚሰጠው ውሃና ፍሳሽ አገልግሎቶች የከተማዋ ህብረተሰብ ረክቶ ማየት እና በዘርፉ የአፍሪካ ከተሞች የልዕቀት ማዕከል ሆኖ መገኘት፡፡
R||divi||400

ተልዕኮ

የጋራ ተጠቃሚነትን መርህ በማድረግ የውሃ መገኛዎችን በማልማት፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓትን በመዘርጋት ፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት፣ ከአዲስ አበባ ከተማ ፈጣን ዕድገት ጋር የሚመጣጠን የንፁህ ውሃ አቅርቦት እና የዘመናዊ ፍሳሽ ማስወገድ አገልግሎት ለከተማዋ ነዋሪ በበቂና አስተማማኝ ሁኔታ መስጠት፡፡
R||divi||400

እሴቶች

1. አገልጋይነት 2. ቅንነት 3. በጋራ መስራት 4. እውቅና መስጠት 5. ልዕቀት 6. ለአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ትኩረት የሚሰጥ 7. ፍትሃዊነት 8. እምነት የሚጣልበት
በባለስልጣኑ ለፍሳሽ ባለሙያዎች ዕውቅና ሰጠ፡፡

በባለስልጣኑ ለፍሳሽ ባለሙያዎች ዕውቅና ሰጠ፡፡

ባለስልጣኑ እውቅና እና ምስጋና መርሃ ግብር ያዘጋጀው ለፍሳሽ ተሽከርካሪ ኦፕሬተሮች እና ረዳቶች እንዲሁም ለሌሎች ባለሙያዎች ነው፡፡ በዕውቅና እና ምስጋና መርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ዘሪሁን አባተ እንደገለጹት፤ ዘርፉ የከተማችን ውበት እና ጽዳት የጀርባ አጥንት እንደመሆኑ እና አሁን ባለው የከተማችን ነባራዊ ሁኔታ አብዛኛው ፍሳሽ ቆሻሻ በተሸከርካሪ የሚነሳ በመሆኑ...

read more
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ የባለስልጣኑን መሰረተ ልማት ጎበኙ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ የባለስልጣኑን መሰረተ ልማት ጎበኙ፡፡

ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ የለገዳዲ ግድብ ማስተንፈሻ በሮች ጥገና ፕሮጀክት ፣ የተፋሰስ ልማት እና የማሰልጠኛ ተቋም ስራዎች በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ በስፋራው ተገኝተው ጎብኝተዋል፡፡ አቶ ጃንጥራር በዚሁ ወቅት ከባህዳር የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የመስክ ላይ የአመራርነት ስልጠና (FLL) ለወሰዱ ሰራተኞችም የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል፡፡ በግድቡ አካባቢ የተሰራው የተፋሰስ ልማት ስራ በጥሩ ደረጃ እንደሚገኝ...

read more

ባለሥልጣኑ 36ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 42ኛው የሥራ አስፈጻሚ ም/ቤት ስብሰባ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት አድርጓል፡፡

ከፊታችን የካተቲ ስምንት እስከ አስራ ሁለት ድረስ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የሥራ አስፈጻሚ ም/ቤት ስብሰባ እንደሚካሄድ ይታወቃል፡፡ ይህ ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ባለሥልጣኑ በዘጠኙም ቅ/ጽ/ቤቶችና በዋና መ/ቤት 24 ሰዓት በተጠንቀቅ የሚሰራ ኮሚቴ አቋቁሞ ወደ ስራ ገብቷል፡፡ ባለሥልጣኑ ለእንግዶች ማረፊያ ለተዘጋጁ 143 ሆቴሎች፣ የስብሰባ አዳራሽ እና 28 ኤምባሲዎች አስፈላጊዉን አገልግሎት ለመስጠት...

read more

ኢንጂነር ዘሪሁን አባተ

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ዋና ስራ አስኪያጅ

መልእክት

የተቋሙ ተገልጋዮች

||divi||400

የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፤

||divi||400

በከተማዋ የሚገኙ የሀገር ውስጥና አለም አቀፋዊ ተቋማት፤

||divi||400

በውሃ መገኛዎች አካባቢ የሚኖሩ የኦሮሚያ ክልል ነዋሪዎች፤

በላይ ደንበኞች

በላይ ሰራተኞች

ቅርንጫፎች

ግድቦች