ዜና
AAWSA joins newly created change management initiative, the FLL Delivery Network.
Field-Level Leadership (FLL) is a values-driven change management approach with a growing record of being able to mobilize staff across the ranks of public water agencies, translating their motivation into systemic and significant performance improvements at the...
ከ25,000 በላይ አዳዲስ አባ እና እማወራዎች የዘመናዊ ፍሳሽ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በበጀት ዓመቱ 6 ወራት ለ25,478 አበወራዎች የፍሳሽ መስመር ቅጥያ በማከናወን ዘመናዊ የፍሳሽ አገልግሎት ተጠቃሚነትን ማረጋገጡ ተገለፀ፣ በመንፈቅ-ዓመቱ ለ14,385 አባወራዎች የፍሳሽ መስመር ለመቀጠል ታቅዶ ለ25,478 አባወራዎች ቅጥያ በማከናወን የፍሳሽ መስመር አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ በ2017 የመጀመርያው ግማሽ ዓመት የተከናወነው የፍሳሽ መስመር ቅጥያ ከዓምናው...
በሰዎች አስተሳሰብ ላይ መስራት ለሁለንተናዊ ለውጥ ትልቅ ድርሻ አለው አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ፡፡
ዋና ስራ አስኪያጁ ይህንን ያሉት ዛሬ በአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የገዳዲ ማሰልጠኛ ተቋም ስልጠና የወሰዱ ሰልጣኞች ባስመረቁበት ወቅት ነው፡፡የሰዎች አስተሳሰብ ላይ ካልተሰራ የህንጻም ሆነ የቴክኖሎጂ ጋጋታ ትርጉም የለውም ያሉት ዋና ስራ አስኪያጁ እንደ ከተማ አስተዳደር ተቋማት በሰው ሃይል መገንባት አለባቸው ተብሎ እየተሰራ ያለውን ስራ የሚያግዝ እና ተስፋ የሚሰጥ ስራ በባለስልጣኑ እየተሰራ መሆኑን ከሰልጣኞች...
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪጅ አቶ ጥራቱ በየነ የባለስልጣኑን አረንጓዴ ልማት ስራዎች ጎበኙ፡፡
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በለገዳዲ ፣ ድሬ እና ገፈርሳ ግድቦች ዙሪያ የተፋሰስ ልማት ስራዎች እየሰራ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ዋና ስራ አስኪያጁ እና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በዛሬው እለት ከዚህ ቀደም በግድቡ ዙሪያ የለሙ ገበያ ተኮር ፍራፍሬዎችን እና የባለስልጣኑ የችግኝ ማዘጋጃ ስፍራ ጎብኝተዋል፡፡በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት ተቋሙ...
ባለስልጣኑ በመጪው የክረምት ወቅት ከ20 ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል አዘጋጅቷል፡፡
ባለሥልጣኑ በውሃ መገኛ አካባቢዎችን የተፋሰስ ልማት ስራ በትኩረት እያከናወነ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሰረት በመጪው የክረምት ወቅት ከ20 ሺህ በላይ የተለያዩ ችግኞች ለተከላ አዘጋጅቷል፡፡ በባለሥልጣኑ የተፋሰስ አስተዳደር እና ጥበቃ ዱቪዥን ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ ታዬ 15 ማሕበራት ያሉት በሰው ሃይል እና በመሳሪያ የተደራጀ የችግኝ ጣቢያ በማቋቋም የሐበሻ እና የፈረንጅ ጽድ፣ ሸውሸዌ፣ ብራዚሊያ፣ እና ግራር የመሳሰሉ ችግኞች ለተከላ...
ባለሥጣኑ ባለፉት 9 ወራት ከ28 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ ፍሳሽ ቆሻሻ አጣርቶ አስወግዷል።
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ፍሳሽ ቆሻሻን በዘመናዊ መንገድ (በመስመር) እና በተሽከርካሪ በማሰባሰብ ከ28 ሚሊዮን ሜ.ኩብ በላይ ፍሳሽ ቆሻሻ አጣርቶ አስወግዷል ።ባለስልጣኑ በዘመናዊ መንገድ ፍሳሽ የማሰባሰብ ስራን ከፍ ለማድረግም የ134.56 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ መስመር ጥናትና ዲዛይን ስራ ያጠናወቀቀ ሲሆን 82.41 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ መስመር ዝርጋታም አከናውኗል፡፡ ባለሥልጣኑ የፍሳሽ አገልግሎቱን ለማፋጠን...
ባለስልጣኑ ባለፉት 9 ወራት 140.3 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ አምርቶ አሰራጭቷል፡፡
ባለስልጣኑ ከገፀ ምድር እና ከርሰ ምድር የውሃ መገኛዎች አለም አቀፍ ጥራቱን የጠበቀ 140.3 ሚሊዮን ሜ. ኪ ውሃ አምርቶ ማስራጨት መቻሉ ተገልጿል ። ከገጸ ምድር የውሃ መገኛዎች 55.75 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ እንዲሁም ከከርሰ ምድር የውሃ መገኛዎች 84.58 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ በማምረት ለነዋሪዎች ተደራሽ ለማድረግ ተችሏል ፡፡ ይህም ከእቅዱ 85 % ያህል ሲሆን የእቅዱን ያክል ማሳካት ያልተቻለው በኤሌክትሮ ሜካኒካል...
ባለለስልጣኑ የሲቢሉ የውሃ ግድብ ፕሮጀክት ፋይናንስ እንዲያደርግ የአለም ባንክን ጠየቀ፡፡
በአለም ባንክ የውሃ ሲንየር ግሎባል ዳይሬክተር ሳሮጅ ኩማር ጃህ የተመራው ልኡክ ዛሬ የድሬ እና ለገዳዲ ግድብ ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝቱ ወቅት የሲቢሉ ግድብ ፕሮጀክት የፋይናንስ ጉዳይ እና በባንኩ የገንዘብ ድጋፍ የሚሰራውን የግድቡ ውሃ ማስተንፈሻ በሮች ጥገና ስራ ላይ ያተኮረ ውይይትም ተደርጓል፡፡ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ዘሪሁን አባተ የአለም ባንክ ግሩፕ ለባለስልጣኑ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አድንቀው፤...
በባለስልጣኑ ለፍሳሽ ባለሙያዎች ዕውቅና ሰጠ፡፡
ባለስልጣኑ እውቅና እና ምስጋና መርሃ ግብር ያዘጋጀው ለፍሳሽ ተሽከርካሪ ኦፕሬተሮች እና ረዳቶች እንዲሁም ለሌሎች ባለሙያዎች ነው፡፡ በዕውቅና እና ምስጋና መርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ዘሪሁን አባተ እንደገለጹት፤ ዘርፉ የከተማችን ውበት እና ጽዳት የጀርባ አጥንት እንደመሆኑ እና አሁን ባለው የከተማችን ነባራዊ ሁኔታ አብዛኛው ፍሳሽ ቆሻሻ በተሸከርካሪ የሚነሳ በመሆኑ...
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ የባለስልጣኑን መሰረተ ልማት ጎበኙ፡፡
ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ የለገዳዲ ግድብ ማስተንፈሻ በሮች ጥገና ፕሮጀክት ፣ የተፋሰስ ልማት እና የማሰልጠኛ ተቋም ስራዎች በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ በስፋራው ተገኝተው ጎብኝተዋል፡፡ አቶ ጃንጥራር በዚሁ ወቅት ከባህዳር የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የመስክ ላይ የአመራርነት ስልጠና (FLL) ለወሰዱ ሰራተኞችም የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል፡፡ በግድቡ አካባቢ የተሰራው የተፋሰስ ልማት ስራ በጥሩ ደረጃ እንደሚገኝ...