ከ25,000 በላይ አዳዲስ አባ እና እማወራዎች የዘመናዊ ፍሳሽ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በበጀት ዓመቱ 6 ወራት ለ25,478 አበወራዎች የፍሳሽ መስመር ቅጥያ በማከናወን ዘመናዊ የፍሳሽ አገልግሎት ተጠቃሚነትን ማረጋገጡ ተገለፀ፣ በመንፈቅ-ዓመቱ ለ14,385 አባወራዎች የፍሳሽ መስመር ለመቀጠል ታቅዶ ለ25,478 አባወራዎች ቅጥያ በማከናወን የፍሳሽ መስመር አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ በ2017 የመጀመርያው ግማሽ ዓመት የተከናወነው የፍሳሽ መስመር ቅጥያ ከዓምናው...

በሰዎች አስተሳሰብ ላይ መስራት ለሁለንተናዊ ለውጥ ትልቅ ድርሻ አለው አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ፡፡

ዋና ስራ አስኪያጁ ይህንን ያሉት ዛሬ በአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የገዳዲ ማሰልጠኛ ተቋም ስልጠና የወሰዱ ሰልጣኞች ባስመረቁበት ወቅት ነው፡፡የሰዎች አስተሳሰብ ላይ ካልተሰራ የህንጻም ሆነ የቴክኖሎጂ ጋጋታ ትርጉም የለውም ያሉት ዋና ስራ አስኪያጁ እንደ ከተማ አስተዳደር ተቋማት በሰው ሃይል መገንባት አለባቸው ተብሎ እየተሰራ ያለውን ስራ የሚያግዝ እና ተስፋ የሚሰጥ ስራ በባለስልጣኑ እየተሰራ መሆኑን ከሰልጣኞች...

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪጅ አቶ ጥራቱ በየነ የባለስልጣኑን አረንጓዴ ልማት ስራዎች ጎበኙ፡፡

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በለገዳዲ ፣ ድሬ እና ገፈርሳ ግድቦች ዙሪያ የተፋሰስ ልማት ስራዎች እየሰራ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ዋና ስራ አስኪያጁ እና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በዛሬው እለት ከዚህ ቀደም በግድቡ ዙሪያ የለሙ ገበያ ተኮር ፍራፍሬዎችን እና የባለስልጣኑ የችግኝ ማዘጋጃ ስፍራ ጎብኝተዋል፡፡በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት ተቋሙ...

ባለስልጣኑ በመጪው የክረምት ወቅት ከ20 ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል አዘጋጅቷል፡፡

ባለሥልጣኑ በውሃ መገኛ አካባቢዎችን የተፋሰስ ልማት ስራ በትኩረት እያከናወነ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሰረት በመጪው የክረምት ወቅት ከ20 ሺህ በላይ የተለያዩ ችግኞች ለተከላ አዘጋጅቷል፡፡ በባለሥልጣኑ የተፋሰስ አስተዳደር እና ጥበቃ ዱቪዥን ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ ታዬ 15 ማሕበራት ያሉት በሰው ሃይል እና በመሳሪያ የተደራጀ የችግኝ ጣቢያ በማቋቋም የሐበሻ እና የፈረንጅ ጽድ፣ ሸውሸዌ፣ ብራዚሊያ፣ እና ግራር የመሳሰሉ ችግኞች ለተከላ...