ጣፎ አደባባይ አካባቢ የሚገኝ የየካ አባዶ ሳይት የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ መስመር ባልተገባ አጠቃቀም ምክኒያት ተዘግቶ ፍሳሹ እየገነፈለ ለነዋሪዉ ፈተና ፤ለአላፊ አግዳሚው ለመጥፎ ጠረን ዳርጎ ሰነባብቷል፡፡ፍሳሹም በማንሆል ገንፍሎ መንገድ ላይ በመፍሰሱ ምክኒንያት ነዋሪዎች ቅሬታ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡ከስፍራው የፍሳሽ ቆሻሻ ሰብስቦ ወደ ኮተቤ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ የሚያጓጉዘው ከፍተኛ የፍሳሽ መስመር መዘጋትን ተከትሎ ችግሩን ለመቅረፍ በተደጋሚ የመስመር ጽዳት ቢያደርግም ችግሩን ሙሉ ለሙሉ መቅረፍ አልተቻለም ነበር፡፡ባለስልጣኑ የችግሩን ግዝፈት በመረዳት ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ክፍተኛ ርብርብ ማድረጉን የፍሳሽ ከፍተኛ መስመር ዝርጋታ ጥገና እና መረብ ቁጥጥር ንዑስ የስራ ሂደት መሪ አቶ አቦነህ ባዩ ተናግረዋል፡፡የፍሳሽ መስመሩ የተዘረጋበት ጥልቀት እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ መስመሩን ፈልጎ ችግሩን ለመለየት እስከ 14 ሜትር ጥልቅት መቆፈር፣ በዚሁ ጥልቀት ላይ ባልታወቀ ምክንያት የፍሳሽ መስመሩ ከ6 ሜትር በላይ ተሰብሮ መገኘቱን ብሎም በአካባቢው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሀይል ተሸካሚ ምሶሶ መኖሩ ስራውን ውስብስብ እንዳደረገው አቶ አቦነህ አብራርተዋል፡፡የባለስልጣኑ የፍሳሽ ዘርፉ ሰራተኞች ቀን ከሌት በመስራት ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ የጥገና ስራው ሙሉ በሙሉ ማከናወን ተችሏል፡፡ተንዶ የነበረውን 12 ሜትር ርዝመት በ4 ሜትር ከፍታ የፍሳሽ መስመር የድጋፍ ግንብ እንደገና በመገንባት የፍሳሽ መስመሩ ያለችግር ተግባሩን እንዲያከናውን ተደርጎ የአካባቢው ችግር ተፈቷል፡፡አቶ አቦነህ የአካቢው ነዋሪዎች በፍሳሽ መስመር ውስጥ መግባት የሌለባቸው ጠጣር ነገሮችን በመጨመር ከፍተኛ ችግር መፍጠራቸውን በመረዳት ለመሰረተ ልማቱ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላፈዋል፡፡
Recent Posts
- በባለስልጣኑ ለፍሳሽ ባለሙያዎች ዕውቅና ሰጠ፡፡
- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ የባለስልጣኑን መሰረተ ልማት ጎበኙ፡፡
- ባለሥልጣኑ 36ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 42ኛው የሥራ አስፈጻሚ ም/ቤት ስብሰባ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት አድርጓል፡፡
- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሥራ አስኪያጅ ዘርፍ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት የኮሙኒኬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች የባለሥልጣኑ መሠረተ ልማቶች ጎብኝተዋል።
- ባለስልጣኑ ባለፉት 6 ወራት 94.2 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ወሃ አምርቶ አስራጭቷል፡፡
Archives
- February 2023
- January 2023
- September 2022
- July 2022
- June 2022
- May 2022
- April 2022
- March 2022
- January 2022
- December 2021
- November 2021
- April 2021
- February 2021
- December 2020
- November 2020
- October 2020
- September 2020
- June 2020
- April 2020
- March 2020
- December 2019
- November 2019
- October 2019
- September 2019
- August 2019
- July 2019
- June 2019
- May 2019
- April 2019
- March 2019
- February 2019
- January 2019
- December 2018
- August 2018
- May 2018
- March 2018
- February 2018
- January 2018
- December 2017
- November 2017
- October 2017
- August 2017
- May 2016
Recent Comments