የ“ካይዘን” ፍልስፍናን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ አዲስ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመረቂ ውጤት እንዳስመዘገበ ተገለጸ

አዲስ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የካይዘን ፍልስፍናን መልካም አስተዳደርን ለማስፈን፣ ህብረተሰቡን ለማርካት እና ለሰራተኛው ምቹ የስራ ቦታ ለመፍጠር እንዲሁም ስር ነቀል የአመለካከት ለውጥ ለማምጣት እየተጠቀመበት እንደሆነ ገለጸ፡፡ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የካይዘን ፍልስፍና ተግባራዊ በማድረጉ የአገልግለት አሰጣጡን ከፍ ማድረግ መቻሉ ተጠቁመሟል፡፡