ለወገን ደራሽ ወገን በመሆኑ ሙሉ ጤነኛ የሆነ ማንኛውም ዜጋ በየ 3 ወሩ ደም ቢለግስ የአዕምሮ እርካታ ከማግኘቱ በተጨማሪ በወሊድ ምክንያት ደም አጥተው የሚሞቱ እናቶቻችን እና በተለያየ ምክንያት ለአደጋ የተጋለጡ ግለሰቦችን ህይወት መታደግ ይቻላል፡፡

“እኛ ጤናማ ሆነን ደም ካልሰጠን የታመሙትን ማዳን አንችልም…!” ያሉት የባለስልጣኑ ሠራተኞች በደም እጦት ምክንያት ህይታቸውን ማትረፍ ለማይችሉ ዜጎች እንዲውል በበጎ ፈቃደኝነት ደም ለግሰዋል፡፡

የደም ልገሳውም ዛሬ በዋናው መ/ቤት የተደረገ ሲሆን፣ በ8ቱም በቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች የሚቀጥል ይሆናል፡፡