ከውሃ መስመር ላይ የሚፈስ እና የሚባክን ውሃን ለመቀነስ ጥረት እየተደረገ ነው::

ከመጠጥ ውሃ ስርጭት መስመር ላይ በሚባክነው ውሃ ዙሪያ ግንዛቤ ለመፍጠር የአለም አቀፍ ውሃ ብክነት ቀን ዛሬ ህዳር 25 ቀን በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀን 346 ቢሊየን ሊትር ውሃ ከውሃ ማሰራጫ መስመሮች ላይ ይባክናል፡፡ ይህን ብክነት በ30% መቀነስ ቢቻል በምድራችን 800 ሚሊየን የሚሆኑ ሰዎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚቻል በዓለም አቀፍ ውሃ ማህበር የውሃ ብክነት ቡድን መረጃ ያመለክታል፡፡ የአዲስ...
ባለስልጣኑ መካኒሳ፣ ጉርድ ሾላ፣ አራዳ እና መገናኛ ቅ/ጽ/ቤቶች የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ  ዙር የደንበኞች ፎረም  ጉባኤ አካሂደዋል፡፡

ባለስልጣኑ መካኒሳ፣ ጉርድ ሾላ፣ አራዳ እና መገናኛ ቅ/ጽ/ቤቶች የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ዙር የደንበኞች ፎረም ጉባኤ አካሂደዋል፡፡

በጉባኤው ላይ ከመልካም አስተዳደር እና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ተቋሙ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ የተወሰዱ እርምጃዎችን የተመለከተ የሩብ ዓመት ሪፖረት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በውሃ ስርጭት ፣ በዘመናዊ ፍሳሽ አወጋገድ እና በገቢ አሰባሰብ ዙሪያ የተሰሩ ስራዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ በገቢ አሰባሰብ ላይ በርካታ ደንበኞች የመክፈል ባህል ዝቅተኛ በመሆኑ በቅስቀሳ ሲያልፍም እርምጃ በመውሰድ...
የአዲስአበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ሰራተኞች እና አመራሮች ለመከላከያ ሠራዊት ደም ለገሱ።

የአዲስአበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ሰራተኞች እና አመራሮች ለመከላከያ ሠራዊት ደም ለገሱ።

“ደማችን ለጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን” በሚል መሪ ቃል የባለሥልጣኑ ሰራተኞች የሀገር መከላከያ ሰራዊታን ለመደገፍ የደም ልገሳ መርሐ ግብር በመካኒሳ ቅ/ጽ/ቤትና በዋናው መ/ቤት አከናውነዋል። በደም ልገሳ መርሐ ግብሩ ላይ አስተባባሪ የሆኑት የባለሥልጣኑ የሴቶች ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ አልማዝ ኤጀርሳ የደም ልገሳ መርሐ ግብሩ ዓላማ የባለሥልጣኑ ሰራተኞች ህግ በማስከበር ተግባር ላይ ለተሰማራው የመከላከያ...
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ሠራተኞች ለሃገር መከላከያ ሠራዊት ከ14.4 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ።

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ሠራተኞች ለሃገር መከላከያ ሠራዊት ከ14.4 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ።

የባለስልጣኑ ሠራተኞች ለጀግናው የሃገር መከላከያ ሠራዊት የአንድ ወር ደመወዛቸውን 14 ሚሊየን 463 ሺህ 815 ብር ለግሰዋል፡፡ ድጋፉን ያደረጉት በዋናው መስሪያ ቤት እና በስምንቱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚገኙ ቋሚ እና ኮንትራት ሠራተኞች መሆናቸውን በባለስልጣኑ የፋይናንስ ደጋፊ የስራ ሂደት መሪ ወ/ሮ ላቀች አግደው አስታውቀዋል፡፡ ከተጠቀሰው ድጋፍ በተጨማሪም በባለስልጣኑ ስፖርት ኮሚቴ አማካኝነት ሠራተኛው ለስፖርታዊ...

ዛሬ የአለም የመጸዳጃ ቤቶች ቀን ታስቦ ውሏል ፡፡

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣንም ቀኑን በማስመልከት ፍሳሽ ቆሻሻን በዘመናዊ መንገድ አጣርቶ የማስወገድ አገልግሎት ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገልጸል፡፡ ባለሥልጣኑ አሁን ያለው ፍሳሽ ቆሻሻን በዘመናዊ መንገድ የማጣራት አቅም በቀን 148 ሺህ ሜ.ኩብ ማድረስ ችሏል፡፡ በዘመናዊ መንገድ ፍሳሽ ሰብስቦ የማጣራት አቅሙ ከፍ ያደረጉት በአሁኑ ሰዓት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የቃሊቲ ፣ የኮተቤ ፣ ሚኪላንድ፣ ገላን እንዲሁም...