የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የትራንስፖርት እና መሰረተ ልማት ቆሚ ኮሚቴ የውሃ እና ፍሳሽ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ ፡፡

ቋሚ ኮሚቴው የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን እያሰራው የሚገኘውን የሳውዝ አያት ኖርዝ ፈንታ የውሃ ፕሮጀክት እና የኮዬ ፈጬን ያልተማከለ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ባሳለፍነው ቅዳሜ ነው የመስክ ጉብኝት ያደረገው ፡፡ የተጎበኘው የሳውዝ አያት ኖርዝ ፈንታ የውሃ ፕሮጀክት ፊዚካል ግንባታ 70 በመቶ የደረሰ ሲሆን ሲጠናቀቅ 68 ሺህ ሜ.ኪዩብ በቀን የማምረት አቅም ያለው እና ከ700ሺኅ በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው...

የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ፍሬህይወት ገብረህይወት ዛሬ የለገዳዲ ግድብ ማጣሪያ ጣቢያ እና በግድቡ ዙሪያ እየተሰሩ ያሉ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸው ወቅትም ባለስልጣኑ እያካሄዳቸው ያሉት ተግባራት መልካም መሆናቸውን ጠቅሰው በቀጣይ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡ በሂደቱም ቢሯቸው ለባለስልጣኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል፡፡ የባለስልጣኑ ዋና ስራስኪያጅ ኢንጅነር ዘርይሁን አባተ ባለስልጣኑ ከገጸ ምድር የሚያገኛቸውን የውሃ ሀብቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ለማድረግ በአከባቢ ጥበቃ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ እስካሁን በድሬ እና...

የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን ደንበኞች ከህገ ወጥ ግለሰቦች ራሳቸውን እንዲጠብቁ አሳሰበ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለስልጣን ከሰጠው ኃላፊነት አንዱ እና ዋነኛው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ንፁህ የመጠጥ ውኃን ለነዋሪ እንዲያዳርስ ነው፡፡ ባለስልጣኑ የተሰጠውን ኃላፊነት ለመወጣት ንፁህ የመጠጥ ውኃ አምርቶ ከማሰራጨት ባለፈ በየቀኑ ከየአካባቢው የውኃ ናሙናዎችን በመውሰድ በላቦራቶሪ ምርመራ የጥራት ደረጃውን ይፈትሻል፡፡ ፍተሻ ከሚደረግባቸው የውኃ ናሙናዎች መካከል የብክለት...

ከሶስተኛ ወለል በላይ ለሚኖሩ የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች ውሃ በፍታዊነት ለማዳረስ የሚያስችል አሰራር ተዘረጋ ፡፡

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የንፋስ ስልክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለነዋሪዎች የሚያሰራጨውን ውሃ በፍታዊነት ለማዳረስ አንዱ የሆነውን የውሃ የግፊት ችግር ለመቅረፍ የዚሁ ሰለባ ከሆኑ የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች ጋር በመተባበር መስራት ጀምሯል ፡፡ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በኦሎምፒያ ኮዶሚኒየም ሶስተኛ እና አራተኛ ወለል ነዋሪዎች እስከ 10ሺህ ሊትር የሚይዝ ሮቶ በመትከል እና ፓምፕ በማዘጋጀት በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በተዘረጋ...